Tuesday, June 4, 2013

  • የታክሲ ከሌለህ ወርደህ በባስ ሂድ
  •  ሠውን ማመን ተፈራርሞ ነው
  • ፍቅር ካለ ባጃጅ ባስ ይሆናል
  •  በቴሌቶን ሂሳብ መክፈል ክልክል ነው
  • ሒሳብ ሳይከፍሉ ሀሳብ አይጀምሩ
  • ለፀባይኛ ተሳፋሪ የፀባይ ዋንጫ እንሸላማለን
  • ለስራ ነው የወጣነው
  • በመጀመሪያ የጋለ ደምህን ተቆጣጠርና ሀሳብህን ግለፅ
  • ባለጌና ዋንጫ ከወደአፉ ይሠፋል
  • ኤች.አይ.ቪንና የጫማ ሽታን በጋራ እንከላከል
  • ማንችስተር ያሸንፋል አርሠናል ለዘለዓለም ይኑር
  • ሠው አካውንት ይከፍታል አንዳንዱ አፉን ይከፍታል
  • ሞባይል ለጣለ ሲም እንመልሳለን
  • ሹፌሩን መጥበስ ክልክል ነው በነገር
  • ሠው ብቻ ነው የምንጭነው በስህተት የገባ ይውረድ
  • ታክሲ ለሚጠቀሙ ብቻ 
  • ክቡራን ተሳፋሪዎቻችን በአገልግሎት አሰጣጣችን ላይ አስተያየት፣ቅሬታ፣ትዝብት ወይም መሻሻል አለበት የምትሉት ነገር ካለ     አንቀበልም!! መውረድ ይቻላል::
  • ለሠው ቅን ሁን እንጂ ቅንቅን አትሁን
  • ማስቲካ የሚታደል መስሎአችሁ አፋችሁን እንዳትከፍቱ
  • መስኮቱን በመክፈት ለትራፊክ ፖሊስ አያጋፍጡን!
  • ጤነኛ ካልሆኑ መውረጃዎ ደርሷል
  • በጭነት መኪና መታችሁ እዚህ ትቀናጣላችሁ
  • የክፍለ ከተማ ሠዎች ካላችሁ ሒሳብ በቅድሚያ
  • ኑሮአችሁ ሳይሞላ "ታክሲው አልሞላም?! " ትላላችሁ!· 
  •  ጥብቅ ማሳሰቢያ ለክቡራን ሌቦች ሒሳብ ሰብስበን ሳንጨርስ ስራችሁን መጀመር አትችሉም! የማይስማማ ሌባ ካለ መውረድ ይችላል
  • ለዓለም ሙቀት መጨመር መንስዔው ጭቅጭቅ ነው
  • ይህ ታፔላ የሚሉት ከመጣ ፤ ምሳችን በቆሎ ራታችን ቂጣ
  • ታክሲው ሳይቆም መውረድ ይቻላል
  •  እንዴት ጭት አትቃሙ ይባላል፣ ሰርቶ የማይዝናና አህያ ብቻ ነው
  • የበታችነት ከተሰማህ ዛፍ ላይ ውጣ
  • ስልጣን ህዝብን ማገልገያ እንጂ ማስፈራሪያ አይደለም
  • የቤትህን አመል እዛው!!!
  • የሠው ትርፍ የለውም . . . ተጠጋጉ!
  • በታክሲ. . . . .  ህግ አላውቅም
  • ታክሲና መንግስተ ሰማያት ሞልቶ አያውቅም
  • ለታላቅ መልስ አይሰጥም
  • ነገን ለመኖር መጀመሪያ ዛሬን ኑር..በመቃም
  • ‹‹ደሀ›› ከፍ ብሎ የሚታየው ባስ ላይ እና እራሱን ሲሰቅል ብቻ ነው፡፡
  • እባክዎን የአባይ ቃል ስላለብን ጠጋ ጠጋ ይበሉልን
  • ለካፌና ለላዳ ብዙ ይከፍላሉ፤ እኛ ጋ ሲሳፈሩ ለምን ይጨቃጨቃሉ