Monday, March 11, 2013



 
በገጣሚና ሰዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ

ያዘቀጠው አሰር እየደፈረሰ
የተቀጣጠለው. . . እንጨቱ እየጨሰ
መሬት ቁና ሁና የሰው ልጅ ሲጨንቀው
እሳት ተያይዞ አገሩን ሲያለብሰው
ባለቤት ተሰዶ አዱኛ ፈራርሳ
አሞራ ሲያንዣብብ ተከምሮ ሬሳ
ስጋ ሲርበደበድ. . . ነፍስ ይሽቆጠቆጣል
ያኔ እያቀዘፈው ደም ይገነፍላል፡፡
ኮሽ ባለ ቁጥር ዞሮ ሲገላመጥ
እየተንሻተተ ገደሉን ሲባጥጥ
ሲቃትት ሲደክም ሲርበው ሲጠማው
ስጋውን በመካድ ሞትን ይመኛል ሰው፡፡
የፍቅር ጥላ ነው  ጭጋግ የደስ. . .ታ
ሀዘን መንገላታት፤ መታሰር መቸገር
    መቁሰል መሰቃየት የሌለው
ፀጥታ

ያንድነት እከክ ነው ልብሱ የነተበ
በላብ በጭቅቅት ገላው የረጠበ
ተለዋዋጭ መልኩ ያልታወቀ ግቡ
አልቋል ሞቷል ሲሉት ያው ይነትራል ልቡ፡፡
ስጋ ተለያይቶ ሲቀር አጥንታቸው
ማንንም በስሙ መጥራት የማንችለው
መልካቸው ሲጠፋ ሁነው እንዳልነበር
እነሆ ርስታቸው የእኩል ቤት መቃብር፡፡
መድፍ የተከላቸው መትረየስ ዘርዝሮ
ቦምብ የመገባቸው አውሮፕላን በሮ፤
ታንክ በደነጎረው ጠመንጃ ዘርቷቸው
ጢስ ወሀ እየሆነ ሲጠጡ ባፋቸው
የታል የበቀሉት ወዴት ነው ቦታቸው?
ሐውልቱ ድንጋዩ ምን አጎነቆለ
     ባንድ በኩል ደግሞ
     የሰላም ሚዛን ነው
     የበዛን አረም
     የሚያስተካክለው፡፡
ሰላም ብዙ ሲቆይ ስሩ ያሻግታል
መሰረቱ ዝጎ ቀስ ብሎ ይወድቃል፤
አንስቶ በመካብ የፈራረሰውን
ቀብሮ በመለሰን. .  .ሲያድስ መሰረቱን፤
ኃይለኛ ሲገባ ሲከተል ዓላማ
ባለህ እርጋ ብሎ አዋጁን ሲያሰማ፤
ይኸው ተጀመረ አዲስ ዓይነት ሰላም
ዳግመኛ እስቲወድቅ ፈርሶ እስቲደመደም፤
ሰላም ያቻት ብሎ ሁሉም የሚጮኸው
ክፉ ቀን አታምጣ ብለን የምንተቸው
በፀሎታችን ውስጥ መሪ እንዳያሳጣን
ወድቀን እንዳንቀር ተገዥ በመሆን፤
ያችት ዓላማችን ነፋስ ተቀበላት
ብለን የምንቆመው ሰላም የምንላት
ፀጥታ ሲኖር ነው አልፈን በጦርነት፤
አንደኛው ሲተኛ ያኛው ሲጠበቀው
ሰላም ወይ ጦርነት ድርና ማግ ናቸው፡፡

ያዘቀጠው አሰር እየደፈረሰ
የተቀጣጠለው. . . እንጨቱ እየጨሰ
መሬት ቁና ሁና የሰው ልጅ ሲጨንቀው
እሳት ተያይዞ አገሩን ሲያለብሰው
ባለቤት ተሰዶ አዱኛ ፈራርሳ
አሞራ ሲያንዣብብ ተከምሮ ሬሳ
ስጋ ሲርበደበድ. . . ነፍስ ይሽቆጠቆጣል
ያኔ እያቀዘፈው ደም ይገነፍላል፡፡
ኮሽ ባለ ቁጥር ዞሮ ሲገላመጥ
እየተንሻተተ ገደሉን ሲባጥጥ
ሲቃትት ሲደክም ሲርበው ሲጠማው
ስጋውን በመካድ ሞትን ይመኛል ሰው፡፡
የፍቅር ጥላ ነው  ጭጋግ የደስ. . .ታ
ሀዘን መንገላታት፤ መታሰር መቸገር
    መቁሰል መሰቃየት የሌለው
ፀጥታ
ያንድነት እከክ ነው ልብሱ የነተበ
በላብ በጭቅቅት ገላው የረጠበ
ተለዋዋጭ መልኩ ያልታወቀ ግቡ
አልቋል ሞቷል ሲሉት ያው ይነትራል ልቡ፡፡
ስጋ ተለያይቶ ሲቀር አጥንታቸው
ማንንም በስሙ መጥራት የማንችለው
መልካቸው ሲጠፋ ሁነው እንዳልነበር
እነሆ ርስታቸው የእኩል ቤት መቃብር፡፡
መድፍ የተከላቸው መትረየስ ዘርዝሮ
ቦምብ የመገባቸው አውሮፕላን በሮ፤
ታንክ በደነጎረው ጠመንጃ ዘርቷቸው
ጢስ ወሀ እየሆነ ሲጠጡ ባፋቸው
የታል የበቀሉት ወዴት ነው ቦታቸው?
ሐውልቱ ድንጋዩ ምን አጎነቆለ
     ባንድ በኩል ደግሞ
     የሰላም ሚዛን ነው
     የበዛን አረም
     የሚያስተካክለው፡፡
ሰላም ብዙ ሲቆይ ስሩ ያሻግታል
መሰረቱ ዝጎ ቀስ ብሎ ይወድቃል፤
አንስቶ በመካብ የፈራረሰውን
ቀብሮ በመለሰን. .  .ሲያድስ መሰረቱን፤
ኃይለኛ ሲገባ ሲከተል ዓላማ
ባለህ እርጋ ብሎ አዋጁን ሲያሰማ፤
ይኸው ተጀመረ አዲስ ዓይነት ሰላም
ዳግመኛ እስቲወድቅ ፈርሶ እስቲደመደም፤
ሰላም ያቻት ብሎ ሁሉም የሚጮኸው
ክፉ ቀን አታምጣ ብለን የምንተቸው
በፀሎታችን ውስጥ መሪ እንዳያሳጣን
ወድቀን እንዳንቀር ተገዥ በመሆን፤
ያችት ዓላማችን ነፋስ ተቀበላት
ብለን የምንቆመው ሰላም የምንላት
ፀጥታ ሲኖር ነው አልፈን በጦርነት፤
አንደኛው ሲተኛ ያኛው ሲጠበቀው
ሰላም ወይ ጦርነት ድርና ማግ ናቸው፡፡

No comments:

Post a Comment