Tuesday, April 23, 2013
Friday, April 12, 2013
አገርን ፍለጋ
የጨርቋን ጫፍ ጥለት
በአቧራ ነትቦ ባንዲራ ያለበት
ጭምድ ድ አርጎ ይዞ ህፃኑ ጠየቀ
ግራ ቀኝ እያየ እየተሳቀቀ
“አገራችሁ ሂዱ” ሰዎቹ የሚሉን
የት ነው አገራችን?
ጥለትሽ ላይ ያለው ያገርሽ መለያ
የት ናት ኢትዮጲያ?
የት ጋር ተጀምራ የት ጋር ነው ምታልቀው?
አፈርና ወንዙ ባህል ሐይማኖቱ ይት ጋር ነው ሚለየው?
በአቧራ ነትቦ ባንዲራ ያለበት
ጭምድ ድ አርጎ ይዞ ህፃኑ ጠየቀ
ግራ ቀኝ እያየ እየተሳቀቀ
“አገራችሁ ሂዱ” ሰዎቹ የሚሉን
የት ነው አገራችን?
ጥለትሽ ላይ ያለው ያገርሽ መለያ
የት ናት ኢትዮጲያ?
የት ጋር ተጀምራ የት ጋር ነው ምታልቀው?
አፈርና ወንዙ ባህል ሐይማኖቱ ይት ጋር ነው ሚለየው?
እዚህ አይደለችም? ወደምንሄድበት እዚያናት ኢትዮጲያ?
ወጥተን ነበር እንዴ ከናታቻን ጉያ?
ውስጥ ሆነን ውጭ ነበርን?
እንደዚ ጨክነው አጣድፈዉ ሚገፉን
ወዴት ነው ምንሄደው?
ወዴት ናት አገሬ?
ወጥተን ነበር እንዴ ከአገር ከድንበሬ?
ኧረ ቆይ እማማ
እስቲ ልጠይቅሽ ጉዳችንን ልስማ
ታላቅ ወንድማችን እውጪ አገር ሚኖረው
እሱም ይባረራል? ጦቢያን ይፈልጋል?
ንገሪኝ እማማ?
ይሄን ነገር ልስማ?!
ወጥተን ነበር እንዴ ከናታቻን ጉያ?
ውስጥ ሆነን ውጭ ነበርን?
እንደዚ ጨክነው አጣድፈዉ ሚገፉን
ወዴት ነው ምንሄደው?
ወዴት ናት አገሬ?
ወጥተን ነበር እንዴ ከአገር ከድንበሬ?
ኧረ ቆይ እማማ
እስቲ ልጠይቅሽ ጉዳችንን ልስማ
ታላቅ ወንድማችን እውጪ አገር ሚኖረው
እሱም ይባረራል? ጦቢያን ይፈልጋል?
ንገሪኝ እማማ?
ይሄን ነገር ልስማ?!
አንድ ምሁር በገበሬው ፊት
አንድ በእርሻ ላይ የሚሠራ ዪኒቨርሲቲ መምህር በገበሬው ዙርያ ጥናት ለመሥራት ወደ
ገጠር ወጡ፡፡ የአካባቢው የገበሬዎች ማኅበርም በአካባቢው የሚኖሩትን ገበሬዎች ለጥናቱ እንዲተባበሩ ለማድረግ ስብሰባ ጠራ፡፡
ምሁሩም ከገበሬዎቹ ፊት ለፊት ተቀመጡና ስለመጡበት ሥራና ከገበሬዎቹ ስለሚጠበቁ ነገሮችም ማብራራት ጀመሩ፡፡
‹‹ጉድ አፍተርኑን፤ እዚህ የመጣነው ፍሮም ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡
ከእናንተ ጋር ሚት ማድረጋችን ጉድ ኦፖርቹኒቲ ነው፡፡ ኦፍ ኮርስ እዚህ ለመምጣት ያሰብነው ቢፎር ኤ
ይር ነበር፡፡ በት አንዳንድ ፕሮሲጀሮችን ለማሟላት ሃርድ ስለሆነብን ትንሽ ሌት
ሆነናል፡፡ ሶሪ፡፡
‹‹የኢትዮጵያ ሜይን ኢንካሟ አግሪካልቸር መሆኑን አንደርስታንድ
ታደርጋላችሁ ብዬ አስባለሁ፡፡ አግሪካልቸር ዋን ኦፍ ዘ ሜይን የሰው ልጆች አንሸንት አክቲቪቲዎች ነው፡፡ ኢን
ኢትዮጵያ ደግሞ ሎንግ ሂስትሪ አለው፡፡ በት አግሪካልቸራችን አንደር ደቨሎፕ ሆኗል፡፡ ፋርሚንጋችን
ፑር ነው፡፡ አክቲቪቴያችን ሌበረስ ነው፡፡ ገበሬው ሳይንቲፊክ ዌይ አይጠቀምም፡፡ ፋርሚንጋችን
ሜካናይዝድ አይደለም፡፡ ገበሬው ኢንፎርሜሽን እንደልቡ አያገኝም፡፡
እነዚህን ኢንፎርሜሽኖች ወሰደን ዳታዎቹን የእናንተን ላይፍ
ለማስተካከል እንጠቀምበታለን፡፡ ኢሪጌሽን ላይና አኒማል ሀዝባንደሪ ላይ ለመሥራት እየተዘጋጀን ነው፡፡ አፍተር
ዛት ደግሞ ሌሎች ላይ እንሄድባቸዋለን፡፡
ታንክ ዩ
ለትብብራችሁ፡፡
ገበሬዎቹ አላጨበጨቡም፤ ራሳቸውንም አልነቀነቁም፡፡
የገበሬ ማኅበሩ ሊቀ መንበር ‹‹እስኪ ጥያቄ ያላችሁ?›› አሉ፡፡
ገበሬዎቹ ዝም አሉ፡፡ ሊቀመንበሩ ደጋግመው ቢጎተጉቱም ገበሬዎቹ ጸጥ አሉ፡፡ በመካከል አንዲት እናት ተነሡና፡፡
‹‹እስኪ የመጡት ሰውዬ ይናገሩና እንጠይቃለን›› አሉ፡፡
ሊቀ መንበሩ ግራ ገባቸውና ‹‹እርሳቸውማኮ ተናገሩ›› አሉ፡፡
‹‹እኛ ግን አልሰማናቸውም›› አሉ እኒያ እናት፡፡
‹‹ታድያ እስካሁን ምን ያደረጉ ነው የመሰላችሁ›› አሉ ሊቀ መንበሩ፡፡
‹‹እኛማ በማናውቀው ቋንቋ የመክፈቻ ጸሎት እያደረሱ ነው የመሰለን›› አሉ፡፡
from dagi views
Subscribe to:
Comments (Atom)
















